የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ራዕይ፤ ተልዕኮና ዕሴቶች
የአስተዳደሩ ራዕይ
- በ1917 ዓ.ም መልካም አስተዳደር የሰፈነበት የህግ እና የታራሚዎች ሰብአዊ መብት የተከነረበት፤የታረመና የታነጸ ፤ አምራች ህግ አክባሪ ዜጋ የሚፈራበት ተቀም ማድረግ፤
የአስተዳደሩ ተልዕኮ
- በፍርድ ቤት ዉሳኔ ወይም ትዕዛዝ ማረፊያና ማረሚያ ቤት የሚላኩ የቀጠሮ እስረኞችና ታራሚዎችን በመቀበል የተጠናከረ የጥበቃ ደህንነት እና አስተዳደር ፤ የመሰረታዊ ፍላጎት አቅርቦት ፤ የተሃድሶና ልማት አገልግሎት በመስጠት ታራሚዎችን የወንጀል አስከፊነት ተረድተዉ አምራችና ህግ አክባሪ ዜጋ እንዲሆኑ በማድረግ ተቀሙ ወንጀልን በመከላከል የህዝብን ሰላምና ደህንነት በማረጋገጥ ረገድ የበኩሉን ድርሻ መወጣት፤
እሴቶች
- የሕግ የበላይነት ማክበር ማስከበር፤
- ሰባአዊ መብት ማክበር ማስከበር፤
- ፍትሃዊነት፤
- ግልጽነትና ተጠያቂነት፤
- ኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስናን መጠየፍ፤
- በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል፤
- ማረም ማነጽ ተኮር አገልግሎት፤
- ለለዉጥ ዝግጁነት፤
- አርአያነት፤
የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ስልጣንና ተግባር
- በፍ/ቤት ዉሳኔ ወይም ትዕዛዝ መሠረት የሚላኩትን ታራሚዎች በመቀበል ይጠብቃል፤ያርማል፤እንዲሁም ከፍ/ቤት የሚሰጡ ዉሳኔዎችን ያስፈጽማል፤
- ታራሚዎችን ፍ/ቤት ያቀርባል፤
- የታራሚዎችን ጤንነት ይጠብቃል፤ነጻ ህክምና ይሰጣል፤ምግብና መጠለያ እንዲያገኙ ያደርጋል፤ለታራሚዎች አካላዊና ስነልቦናዊ እንከብካቤ አስፈላጊ ተግባሮችን አገልግሎቶችንና እንቅስቃሴዎችን ያካሄዳል፤
- ታራሚዎች ከተለቀቁ በሓላ እራሳቸዉን ለማስተዳደና ለህግ ተገዠ እንዲሆኑ የሚያችል የቀለም፤የሙያ ስልጠና፤ማህበራዊ እና የምክር አገልግሎት ያሰጣል፤
- በፍ/ቤት ሲታዘዝ ታራሚዎችን ከፌዴ/ማረ/ቤቶች ወደ ክልል ማረ/ቤቶች አጅቦ ያደርሳል፤
- ለታራሚዎች በማረ/ቤት ቆይታቸዉ የማረ/ቤቱን የስነ ስርአት መመሪያ በመጣስ ለሚፈጸሙ ጥፋት ደንብና መመሪያ በሚያዘዉ መሰረት የስነ ስርአት ቅጣቶችን የወስናል፤ያስፈጽማል፤
- በፌደራል ደረጃ ከየማዕከል ማረ/ቤቶች ታራሚዎች በሚመለከት መረጃዎችንና ስታስቲኮችን ያሰባስባል፤የጠናቅራ፤መረጃ ለሚመለከተዉ አካል ይሰጣል፤
- ታራሚዎች በሚያሳዩት የባህሪ ለዉጥ በሕጉ መሠረት በአመክሮ ወይም በይቅርታ እንዲፈቱ ስልጣን ለተሰጠዉ አካል ሀሳብ ያቀርባል፤
- አስተዳደሩ ለሥራ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኝ የማረሚያ ጥበቃ አባላትን ይመለምላል፤ይቀጥራል፤ያሰለጥናል፤ እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ ሲቪል ሠራተኞችን ይቀጥራል፤ያስተዳድራል፤
- የመ/ቤቱ ሠራተኞች ሙያ ብቃት ለማሣደግ በአገር ዉስጥና በዉጭ አገር የስልጠና እድሎችን ያመቻቻል፤
- የታራሚዎች አጠባበቅና አያያዝ ለማሻሻል የማረሚያ ጥበቃ አባላትን የሙያ ብቃትና አገልግሎት ደረጃዉን የጠበቀ እንዲሆን የሚረዱ ጥረቶችን ያከናዉናል፤
- የፌደራል ማረ/ቤቶች አስተዳደር ከክልል ማ/ቤቶች የሙያ፤ የቴክኒክና የምክር አገልግሎት ይሰጣል፤
- የንብረት ባለቤት ይሆናል፤ዉል ይዋዋላል፤ በራሱ ይከሳል፤ይከሰሳል፤
- ከስራዉ ባህሪዉ ጋር ተያያዝነት ያላቸዉን ሌሎች ተግባራት ያከናዉናል፤

ያንብቡ
ReplyDelete